top of page
DSC_4642_edited.jpg

Welcome to
IEEC Bible College

ወደ IEEC መጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ እንኳን በደህና መጡ

ትምህርት ቤታችን የአዲሱን አመት የሠርተፊኬት ትምህርት ምዝገባ ጀምሯል።

students_edited.jpg

የተማሪ ህይወት

አንድ ክርስትያን ሌሎች ክርስትያኖች ያስፈልጉታል፡፡ በክርስትና ውስጥ ያለሌላው ክርስትያን ተሳትፎ መንፈሳዊ እድገት አይኖርም፡፡ እያንዳንዱም ክርስትያን ከሌላው የሚቀበለውና እራሱም ለሌላው ክርስትያን የሚሰጠው ጸጋ አለው፡፡ ምክንያቱም ክርስትያን የአካሉ (የቤተክርስትያን) አንድ ብልት ነው፡፡ በአካል ውስጥ አንድ ብልት ያለሌሎች ብልቶች ህይወት ሊኖረው አይችልም፡፡ ሌሎችም ብልቶች ይኸ ብልት ያስፈልጋቸዋል፡፡

የዓለምአቀፍ የኢተዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስትያን መጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ (IEECBC) ከምንም በላይ የተማሪዎቹን ክርስትያናዊ መንፈሳዊ ህይወት ለውጥና እድገት አጥብቆ የሚፈልግና ለዚህም የሚሰራ ነው፡፡ ከላይ የተጠቀሱትን መሰረት በማድረግ ተማሪዎች በእየአካባቢያቸው አነስተኛ ቡድኖችን እንዲያቋቁሙና በነዚህ ቡድኖች ውስጥ ሆነው እንዲፀልዩ፣ የእግዚአብሔርን ቃል እንዲከፋፈሉ፣ የቤት ስራቸውን እንዲወያዩበትና፣ ፈተናቸውን አብረው እንዲያጠኑ የመጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጁ አጥብቆ ያበረታታል፡፡

DSC_4668_edited.jpg
bottom of page